Postlar filtri


በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የመድኃኒቶች ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ ያግዛል የተባለዉ አዲስ መመሪያ ወጣ

የኢትዮጵያ ምግብና መድኃኒት ባለሥልጣን በሀገር ውስጥ የሚመረቱ የመድኃኒቶች ጥራትና ደህንነትን ለማረጋገጥ የሚያግዝ አዲስ መመሪያ ማዉጣቱን ካፒታል ጋዜጣ ዘግቧል።

"የባዮኤክቫለንስ ጥናት ማዕከል እና የባዮአናሊቲካል ላብራቶሪ ቁጥጥር መመሪያ ቁጥር 1043/2017" ተብሎ የሚጠራው ይህ መመሪያ፣ በገበያ ላይ የሚውሉ የመድኃኒት ምርቶች ተመሳሳይ የፈዋሽነት እና የደህንነት ደረጃዎችን ማሟላታቸውን ለማረጋገጥ ያለመ መሆኑ ተጠቁሟል።

ይህ መመሪያ "ባዮኢኩዊቫለንስ" የተሰኘ ልዩ ጥናት በማድረግ በጽንስ ስም የሚመረቱ መድኃኒቶች ከታወቁ የመድኃኒት ምርቶች ጋር ያላቸውን ተመሳሳይነት ማረጋገጥ እንደሚጠበቅባቸው ይደነግጋል።በተጨማሪም፣ መመሪያው የመድኃኒት
ማምረቻ ተቋማትና ላቦራቶሪዎች ፈቃድና ቁጥጥር ላይ እንደሚያተኩር  ለመረዳት ችሏል።

VOA Amharic












የወንጀል ቅጣት አወሳሰን ረቂቅ መመሪያ ለተመሳሳይ ወንጀሎች ተቀራራቢ ውሣኔ ማሳለፍ የሚያስችል ነው - የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት

የካቲት 29/2017 በወንጀል ቅጣት አወሳሰን ላይ የተዘጋጀው ረቂቅ መመሪያ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለተመሳሳይ ወንጀሎች ተቀራራቢ ውሳኔ ማሳለፍ የሚያስችል መሆኑን የፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት አስታወቀ።

በተሻሻለው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን ረቂቅ መመሪያ ላይ የቅጣት እርከን ያልነበራቸው የወንጀል አይነቶች መካተታቸውም ተገልጿል።

የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት በወንጀል ቅጣት አወሳሰን ረቂቅ መመሪያ ላይ የክልልና ከተማ አስተዳደር የፍትሕ አካላት በተገኙበት በአዲስ አበባ የውይይት መድረክ አካሂዷል።

በዚሁ ጊዜ የፌደራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ቴዎድሮስ ምህረት፤ የተሻሻለው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን ረቂቅ መመሪያው የፍትሕ ሥርዓቱን ለማሻሻል በሚደረገው ጥረት ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል ብለዋል።

ረቂቅ መመሪያው በወንጀል ቅጣት ውሳኔ አሰጣጥ ሂደት የሚነሱ ቅሬታዎችን በመፍታት የወንጀል ሕጉን ግቦች ማሳካት በሚያስችል መልኩ ተገማች ውሳኔ ማስተላልፍ እንዲቻል መዘጋጀቱን ተናግረዋል።

በተጨማሪም ረቂቅ መመሪያው የቅጣት ደረጃና እርከን ያልነበራቸው ወንጀሎችን በማካተት በፍርድ ቤት የሚሰጡ ውሳኔዎች ተቀራራቢና አስተማሪ እንዲሆኑ የሚያስችል መሆኑንም አስረድተዋል።

ከዚህ ቀደም የቅጣት እርከን ያልወጣላቸው የወንጀል ድርጊቶች በዳኞች ፈቃደ ስልጣን ውሳኔ ሲሰጥ መቆየቱን አስታውሰዋል።

በተሻሻለው የወንጀል ቅጣት አወሳሰን ረቂቅ መመሪያው ላይ በአስገድዶ መድፈር፣ በሰው መግደልና ሌሎች የወንጀል ድርጊቶች የቅጣት እርከን ከፍ እንዲሉ መደረጉን አብራርተዋል።

በዚህም ዳኞች ለተመሳሳይ የወንጀል ድርጊቶች ተቀራራቢ፣ ተገማችና ተዓማኒ ውሳኔ ማሳለፍ የሚያስችላቸው መሆኑን ገልጸዋል።

የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ምክትል ፕሬዝዳንትና የቅጣት አወሳሰን መመሪያ ዝግጅት ኮሚቴ ሰብሳቢ ተክሊት ይመሠል፤ በረቂቅ መመሪያው የቅጣት ደረጃ ያልነበራቸው ወንጀሎች የእርከን ደረጃ ወጥቶላቸዋል ብለዋል።

ረቂቅ መመሪያውም ለተመሳሳይ የወንጀል ድርጊቶች ተቀራራቢና ተገማች ውሳኔ በማሳለፍ የሚያጋጥሙ ክፍተቶችን መሙላት በሚያስችል መልኩ መዘጋጀቱን አስታውቀዋል።

የአደገኛ መርዛማ መድኃኒቶች፣ የአደንዛዥ ዕፅ እና የጦር መሳሪያ ዝውውሮች፣ በቴሌኮምና ኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈጸሙ ወንጀሎች የቅጣት እርከን እንደወጣላቸው ገልጸዋል።

በተጨማሪም ሰውን በሕገ-ወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር፣ የታክስ ማጭበርበር ወንጀሎች ላይ የቅጣት እርከን መውጣቱ ፍርድ ቤቶች አስተማሪና ወጥ የቅጣት ውሳኔ እንዲያሳልፉ ያስችላል ብለዋል። ኢዜአ




በሕጻን ልጅ እገታ ወንጀል የተከሰሱ ግለሰቦች በጽኑ እስራት ተቀጡ።

ባሕር ዳር: የካቲት 29/2017 ዓ.ም በሕጻን ልጅ እገታ ወንጀል የተከሰሱ ግለሰቦች በጽኑ እስራት መቀጣታቸውን የደቡብ ወሎ ዞን ፍትሕ መምሪያ አስታውቋል።

የመደበኛ ወንጀል ጉዳዮች አሥተባባሪ ዳዊት መሠረት ስለወንጀሉ ድርጊት አፈጻጸም እና ቅጣት ውሳኔው እንደተናገሩት አንደኛ ተከሳሸ አንድነት ትርፌ እና ሁለተኛ ተከሳሸ አብርሃም ቢሰጥ አየነው የተባሉ ግለሠቦች ናቸው።

የአራት ዓመት ሕጻን የኾነውን መሐመድ ሰይድን ከደሴ ከተማ ጢጣ አዲሱ ሰፈር ተብሎ ከሚጠራው አካባቢ ከቤተሰቦቹ ጋር በተኛበት በ11/01/2017 ዓ.ም በግምት ከለሊቱ ሰባት ሰዓት አካባቢ በቦንብ በማስፈራራት በኃይል ቤቱን ሰብረው በመግባት ሕጻኑን ከወላጅ እናቱ ነጥለው ወስደዋል ብለዋል።

ከወሰዱ በኋላም ውጪ ሀገር የሚኖረውን ወላጅ አባቱን ከ700 ሺህ ብር እሰከ 1 ሚሊዮን ብር እንዲልክ አድርጊ በማለት ካስጨነቁ በኋላ ድርድሩ አልሳካ ሲል ሕጻኑን ይዘው ቢሰወሩም በፖሊስ ክትትል በ12/01/ 2017 ዓ.ም በደሴ ከተማ ጢጣ እንጨት ተራ አካባቢ ከምሽቱ ሁለት ሰዓት ላይ አጋቾች ከነሕጻኑ ሲንቀሳቀሱ መያዛቸውን ገልጸዋል።

ምርመራውን በጋራ ካጣራን በኋላ የደቡብ ወሎ ዞን ፍትሕ መምሪያ የመደበኛ ወንጀል አቃቢ ሕግ ክሱን በተፋጠነ አቅርቦ የነበረ ቢኾንም ክርክሩ ሲታይ ከቆየ በኋላ የደቡብ ወሎ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የካቲት 27/2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ተከሳሾችን ጥፍተኛ በማለት አንደኛ ተከሳሸ አንድነት ትርፌ በ21 ዓመት ጽኑ እስራት እና ሁለተኛው ተከሳሸ አብርሃም ቢሰጥ በ19 ዓመት ጽኑ እስራት ተወስኖባቸዋል ነው ያሉት።

አሥተባባሪዉ እንደዚህ አይነት የወንጀል ድርጊት በዞናችን ያልተለመደ እና ከባድ ወንጀል በመኾኑ ለእነሱም ኾነ ለሌላዉ ማኅበረሰብ አስተማሪ ነዉ ብለዋል።

አሚኮ






ትብብር እንዲደረግ የቀረበ ጥሪ

“የአማራ ክልል ፍርድ ቤቶች ዳኞች የደመወዝና ጥቅማጥቅም ማሻሻያ” በሚል በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በተለይም በፌስቡክና በቴልግራም ገፆች የተለቀቁ ሰነዶች መኖራቸውን አይተናል።

እነዚህ ሰነዶች አንዳንዶች በፎቶ ሾፕ የተሰሩ አንዳንዶች ደግሞ ገና ያልፀደቁ ረቂቅ ሰነዶች መሆናቸውንም ተገንዝበናል ።

የዚህ አይነቱ ድርጊት እየተፈፀመ ያለው በዋናነት አንዳንድ ሃላፊነት በጎደላቸው በሥራ ላይ ባሉ ዳኞችና ዐቃቢያነ ሕግ ስለመሆኑ እስከአሁን የተሰባሰቡ መረጃዎች እና ማስረጃዎች ያሳያሉ ።

የዚህ አይነቱ ድርጊት የተዛባ መረጃ በማሰራጨት ላልተፈለገ ዓላማ እንዲውል ከማድረግ ባሻገር አጠቃላይ የዳኞችን እና ዐቃቢያነ ሕግን ጥቅም ይጎዳ እንደሆን እንጅ አንዳች የሚያስገኘው ጥቅም የለም ።

በተለይም አብዛኛው ዳኛ በለውጥ ስሜት ውስጥ ሆኖ ተገቢውን የዳኝነት አገልግሎት ለመስጠት ሌት ተቀን እየሰራ ባለበት : የፍ/ቤቶች አመራር እና የክልሉ መንግስት የዳኞችን ጥያቄ ደረጃ በደረጃ እየፈታ እና ለመፍታት ጥረት እያደረገ ባለበት ወቅት የዚህ አይነት አሳፋሪ ድርጎት መፈፀሙ አብዛኛውን ዳኛ ያስቆጣ እንደሆነ ማወቅ ተችሏል።

ስለሆነም በዚህ ድርጊት ዋና ተዋናይ የሆኑ አካላትን በመደበኛው ሕግና በዲስፕሊን ተጠያቂ ለማድረግ በፖሊስና በፍ/ቤቱ በሚመለከተው የሥራ ክፍል የምርመራ ሥራ የተጀመረ ሲሆን ዐቃቢያነ ሕግን በሚመለከት ፍትህ ቢሮ ተመሳሳይ እርምጃ ለመውሰድ እንዲያመቸው ከአስፈላጊ መረጃዎች ጋር ተልኮለታል።

ስለሆነም :-

1. በዚህ ድርጊት የተሳተፉ አካላትን በተመለከተ ተጨማሪ መረጃና ማስረጃ ያላችሁ አካለት በተለያየ መንገድ ለፍ/ቤቱ ጥቆማና ማስረጃ እንድትሰጡ :

2. የተለያየ የሶሻል ሚዲያ አካውንቶች ( በዋናነት ፌስቡክ እና ቴሌግራም) በዳኞች : ዐቀቢያነ ሕግ እና በፍትህ ስም ከፍታችሁ የምታስተዳድሩ ዳኞችና ዐቃቢያነ ሕግ ለምትለጥፍት እና ለምታጋሩት ሰነድ እና መረጃ ሃላፊነቱ በዋናነት የናንተ መሆኑን ተረድታችሁ በሚደረገው ምርመራ ተባባሪ እንድትሆኑ እና ከዚህ አይነት ድርጊት እንድትቆጠቡ

3. በዚህ አይነተ የሶሻል ሚዲያ ስብስቦች ውስጥ ገፆችን የተወዳጃችሁ እና አባል የሆናችሁ ዳኞች የዚህ አይነቱ ድርጊት የሚያመጣውን ሃላፊነት ተረድታችሁ የራሳችሁን ማስተካከያ እንድታድርጉ

ጠቅላይ ፍ/ቤቱ እያሳሰበ : ከፖሊስና ከዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ጋር በመተባበር የተጀመሩ የማጣራት ሥራዎች እንደተጠናቀቁ ተጠያቂነትን የሚያረጋግጥ መሆኑን እንዲሁም ውጤቱንም የሚያሳውቅ መሆኑን እየገለፀ በዚህ የምርመራ ሂደት ሁላችሁም ተባባሪ እንድትሆኑ ጥሪ ያቀርባል ። የአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት


የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ለፍልሰት አስተዳደር ስርዓት መጠናከር በቅንጅት መስራት ይጠበቅባቸዋል - ፍትሕ ሚኒስቴር

አዲስ አበባ፤ የካቲት 28/2017፡- የሲቪል ማሕበረሰብ ድርጅቶች ለፍልሰት አስተዳደር ስርአት መጠናከር በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው ፍትሕ ሚኒስቴር አስታወቀ።

በፍልሰት ዙሪያ የሚሠሩ 27 የሲቪል ማህበረሰብ የሀገር ውስጥ በጎ አድራጎት ድርጅቶች ዛሬ በአዲስ አበባ የጋራ ፎረም መስርተዋል።

የፍትሕ ሚኒስትር ዴኤታ ኤርሚያስ የማነብርሀን(ዶ/ር) በዚሁ ወቅት እንዳሉት፤ ድርጅቶቹ ፎረሙን ማቋቋማቸው የተሻለ አገልግሎት መስጠት ያስችላቸዋል።

ፎረሙ በአጠቃላይ በፍልሰት አስተዳደር ውስጥ ሁሉን አቀፍ የቅንጅት አሰራርን ያጠናክራል ነው ያሉት።

የፍልሰት ጥበቃ ስርዓት ከማጠናከርና ተመላሾችን ወደ ቀያቸው ከመመለስ አኳያም የድርጅቶችን ሚና የላቀ እንደሚያደርገው እንዲሁ።

በተጨማሪም ፎረሙ በፍልሰት አስተዳደር የተግባር ድግግሞሽን እና የሀብት ብክነትን የሚያስቀር ሲሆን የጋራ የመረጃ ልውውጥ ስርዓት መዘርጋት እንደሚያስችላቸው ጠቅሰዋል።

ስምምነቱን ከፈረሙት ድርጅቶች መካከል የአጋር ኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አበራ አደባጆቴ(ዶ/ር)፤ ፎረሙ መመስረቱ በፍልሰት አስተዳደሩ ላይ የተሻለ ስራ መስራት ያስችላል ብለዋል።

ፎረሙን የመሰረቱት ድርጅቶች ቀደም ሲል ስደተኞችን ከቤተሰቦቻቸው በማገናኝት፣ ተጎጂዎችን በተበታተነ መልኩ የመንከባከብና ትምህርትና ስልጠና የመስጠት ስራዎችን የሚያከናውኑ መሆናቸውን ጠቅሰዋል።

ሆኖም ፎረሙ መመስረቱ በተበታተነ መልኩ ሲያከናውኑ የቆዩትን ተግባራት በተቀናጀ መልኩ ለማስኬድ ይረዳናል ነው ያሉት።

ፎረሙ በፍልሰት አስተዳደር ላይ የሚሰሩ ድርጅቶች መካከል ሕብረትና ትብብር እንዲኖር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም ነው የገለጹት።

የአጋር ኢትዮጵያ በጎ አድራጎት ድርጅት ዋና ስራ አስኪያጅ አበራ አደባጆቴ(ዶ/ር) ለሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ፎረሙን በሰብሳቢነት ለመምራት ተመርጠዋል።

ኢዜአ








Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish


ደሴ ጥላሁን (ዶ/ር) የአማራ ክልል የፍትሕ እና ሕግ ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ሆነው ተሾሙ

የካቲት 27/2017፦የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ፤ ደሴ ጥላሁን(ዶ/ር)ን የክልሉ የፍትሕ እና ሕግ ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ አበራን ደግሞ ምክትል ዳይሬክተር አድርገው ሾመዋል፡፡

ተሿሚዎቹ ያላቸውን የካበተ ልምድ፣ ክህሎት እና ዕውቀት በመጠቀም የክልሉን የፍትሕ አሥተዳደር ሥርዓት ለማዘመን እና ለማሻሻል ለሚደረገው ሁለንተናዊ እንቅስቃሴ የበኩላቸውን አሻራ ያሳርፋሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ ተገልጿል፡፡

ለክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ተጠሪ የሆነውን የአማራ ክልል የፍትሕ እና ሕግ ኢንስቲትዩት ፤ የክልሉ ምክር ቤት ከየካቲት 4 እስከ 7 /2017 ዓ.ም ባካሄደው 6ኛ ዙር፣ 4ኛ ዓመት፣ 9ኛ መደበኛ ጉባኤ እንደገና ማቋቋሙ ይታወቃል፡፡

ኢንስቲትዩቱ ብቃት፣ ክህሎት እና መልካም ሥነ ምግባር የተላበሱ የዳኝነት እና የፍትሕ ባለሙያዎችን የማፍራት ተልዕኮውን በአግባቡ እንዲወጣ በማድረግ፣በክልሉ የፍትሕ አሥተዳደር ሥርዓት ላይ ጉልህ መሻሻል እንደሚያመጣ ተገልጿል።

https://www.facebook.com/share/19t88Axp2q/

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.